ይህ ደንብ የተዘጋጀው ታካሚዎች ተገቢውን የህክምና አገልግሎት ማግኘታቸውን ለማረጋገጥና ከህክምና ባለሙያዎች ጋር የሚኖራቸውን ትብብር ጥቅም በማስተዋል ነው:: ስለዚህም የሜዲካል ካውንስል፣ የነርሲንግና የአዋላጅ ነርስ ክፍል፣ የመድሀኒት ክፍል፣ የጥርስ ህክምና ክፍል፣ የአካል ቴራፒ ክፍል፣ የሜዲካል ቴክኖሎጂ ክፍል እንዲሁም የማዳን ጥበብ ኮሚቴ ይሄንን የታካሚዎች መብትና ግዴታ መመሪያ ደንብ እንደሚከተለው ያሳውቃሉ:
7.1. በደንብና በስነ ምግባር መሰረት የሚሰሩ የሜዲካል ሰራተኞች በህጉ መሰረት ጥበቃ ያገኛሉ:: ውሸት ከሆነ ውንጀላ የመጠበቅ መብት አለው/አላት::
7.2 ሜዲካል ፕራክቲስ(የህክምና አገልግሎት) ማለት በዘመኑ ጊዜያዊ እውቀት የተረጋገጠ እንዲሁም ለታካሚዎች ከጉዳት ይልቅ ጥቅም የሚሰጥ ዘመናዊ መድሀኒት ማለት ነው::
7.3 የህክምና አገልግሎት ለሁሉም አይነት በሽታዎች ወይም ሁኔታዎች ፍፁም የሆነ የህክምና ምርመራ, መከላከያ እና እንክብካቤ ላይሰጥ ይችላል::
7.4 የትኛውም የህክምና አገልግሎት የበለጠ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል ጉዳት የሚፈጥርበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል:: በተጨማሪም የህክምንም አገልግሎት ሰጭዎች በየትኛውም አይነት ጥንቃቄ የተሞላበት ሁኔታ ቢሰሩ እንኳን ያልተጠበቀ ጉዳት ሊደርስ ይችላል::
7.5 የትኛውም ማጣሪያ, ምርመራ,እንዲሁም የክትትል አገልግሎት በቴክኖሎጂ እጥረት እንዲሁም በሌሎች መቆጣጠር በማይቻሉ ሁኔታዎች ምክንያት ስህተት ሊፈጠር ይችላል::
7.6 የህክምና አገልግሎት ሰጭዎች የሜዲካል እውቀታቸውን, ችሎታቸውን, ያለውን ውስንነት, አላማ እንዲሁም ሁኔታዎች መሰረት የህክምና አገልግሎቱን በተመለከተ የራሳቸውን ግምታዊ ውሳኔ እንዲሰጡ ይፈቀድላቸዋል:: ይሄም ታካሚውን ማማከርና እንዲሁም ዝውውሩ የታካሚውን መብትና ጥቅም በጠበቀ መልኩ መሆኑ መረጋገጥ አለበት::
7.7 ለታካሚዎች ጥቅም ሲባል በፍላጎታቸው መሰረት የህክምና አገልግሎት ሰጭ ሰራተኞች ለታካሚው ሀሳብ መስጠት ወይም ወደሌላ ክሊኒክ ለተገቢ ህክምና እንዲዘዋወር ሊያደርጉ ይችላሉ:: በዚህ ሁኔታ ታካሚዎች አጣዳፊና ህይወት እስጊ ሁኔታ ላይ መሆን የለባቸውም::
7.8 የህክምና አገልግሎት ሰጭ ሰራተኞች የሜዲካል መረጃ እና እውነት እንዳያውቁ ማድረግ በህክምና አገልግሎቱ ላይ መጥፎ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል::